ኣዲስ ኣበባ
ላለፉት ሶስት ዓመታት እያዝናና ቁምነገር ሲነግረን የቆየው አሁንም በEBC ራድዮ ጣብያ በኤፍኤም 97.1እየተላለፈ የሚገኘው ጣፋጭ ሕይወት የተሰኘው የራድዮ ዝግጅት ሶስተኛ አመቱን አስመልክትቶ እንዲሁም ለመጀመሪያ ጊዜ ጣፋጭ ህይወት የተሰኘ ሽልማት በዛሬው እለት በ ዘ ሃብ (The hub) ሆቴል ደማቅ በሆነ ዝግጅት አካሂዷል በሽልማቱም
ለቡድን በተሰጠ ሽልማት በበጎ ተግባር ከፊት የምንጠራቸው ባየሽ ኮልፌወች ተሸላሚ ሆነዋል
በአነቃቂ ንግግር ተስፋ የምናደርግበት በሚለው ዘርፍ አቶ ማንያዘዋል እሸቱ
አነቃቂ ንግግርን በተግባር ያሳየ በሚለው ዘርፍ አቶ ቴድሮስ ታደሰ
ስራ ፈጠራን በተግባር ያሳየች በሚለው ዘርፍ ወ/ት ሳምራዊት ፍቅሬ
መልካም ተግባር በግለሰብ ወ/ሮ ሙሉ ሀይሌ
በስራ ፈጠራ ተስፋ በሚጣልበት ወጣት ኢዘዲን ከሚል አሸናፊ ሆነዋል
ኢዘዲን ካሚልም ወጣቱ ችግር ፈቺ እንጂ ችግር ፈጣሪ መሆን የለበትም ሲል መልእክቱን አስተላልፏል።
ሽልማቱን ያገኛችሁ በሙሉ እንኳን ደስ ያላችሁ!!
ግንቦት 30